Friday, October 11, 2019

ጠ/ሚ/ር ዶ/ር አቢይ አህመድ የዓለም የሠላም የኖቤል ሽልማት አሸናፊ መሆናቸው ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ለመላው የአፍሪካ ህዝብ ጭምር ታላቅ ኩራት በመሆኑ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የተሰማውን ልባዊ ደስታ ይገልፃል፡፡

Friday, June 7, 2019

በአዲሱ የግንባታ አሠራር አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑ ተገለፀ፡፡ ዜና ግንቦት 29 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽ/ቤት ለሚገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች አስፈላጊው የግንባታ ግብዓት በሥራ ተቋራጮች እየቀረበ ቤቶቹ የሚገነቡበት አሠራር በመዘርጋቱ አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑ ተገለፀ፡፡ አዲሱ አሠራር በቦሌ አራብሳ ሳይት የግንባታ አፈፃፀሙን ለማፋጠን የጎላ አስተፅኦ ማበርከቱን የልደታ ቅርንጫፍ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አመልክቷል፡፡ የቅርንጫፍ ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አረጋ አባተ እንደገለፁት ቀደም ሲል የነበረውን ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የግንባታ ግብዓቶችን እያቀረበ የሚያስገነባበትን አካሄድ በመቀየር ግብዓቶቹ በሥራ ተቋራጮች እየቀረበ ግንባታው የሚካሄድበት አሠራር ተግባራዊ በመደረጉ የተሻለ ለውጥ ማስመዝገብ ተችሏል፡፡ በአዲሱ አሠራር ነው ወደ ሥራ የገባነው ያሉት ዋና ሥራ አስኪያጁ በተለይ ለመንግሥት ሠራተኞች በኪራይ ለማስተላለፍ በባሻ ወልዴ እና በገላን ሳይቶች በንፋስ ስልክ ላፍቶ ቅርንጫፍ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አማካኝነት በመገንባት ላይ ከሚገኙት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ጠቃሚ ልምድ በመውሰድ ወደ ሥራ መገባቱንም ጠቁመዋል፡፡ የበለስ አማካሪ ድርጅት የፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ አሸናፊ ታምራት በበኩላቸው የግንባታ ግብዓቶችን ተቋራጮች እያቀረቡ የሚገነቡበት አዲስ አሠራር መዘርጋቱ ለሥራ ቅልጥፍናም ተመራጭ እንደሆነ አመልክተው ህንፃዎቹን በፍጥነት በማጠናቀቅና ለተጠቃሚዎች ለማድረስ የጎላ አስተዋፅኦ እንዳለው ነው የሚናገሩት፡፡ አዲሱን አሠራር በበለጠ ስኬታማነት ለማከናወን እና ህብረተሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ መንገድ መብራትና ውሃን የመሰሉ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችንም ትኩረት ሰጥቶ ማሟላት እንደሚገባ የሥራ ኃላፊዎቹ አሳስበዋል፡፡

Friday, May 3, 2019

ሚያዚያ 2011 ዜና በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽ/ቤት በተለያዩ ቅርንጫፍ የቤት ልማት ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ላይ ተመድበው የሚሰሩ አማካሪዎች በመሰረት ላይ ያሉትን የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ለማፋጠን አዳዲስ ሀሳቦችን አመንጪ በመሆንና ችግሮችን እየፈቱ መፍትሄ በማስቀመጥ ለግንባታው መፋጠን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ የአ/አ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኪሮስ መሰለ አሳሰቡ፡፡ በአማካሪዎች ዙሪያ እየታዩ ያሉ ችግሮች(የመፍትሄ አቅጣጫዎች) ለማስቀመጥ በተጠራው የውይይት መድረክ ላይ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኪሮስ መሰለ እንደተናገሩት ለመኖሪያ ቤቶች ግንባታ መጓተት የአማካሪው ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ጠቅሰው በተለይም ስኬጅዋል እያወጡ ለኮንትራክተሩ መስጠትና በተሰጠው ጊዜ ሰሌዳ ስራውን ባላከናወነ ተቋራጭና ማህበራት ላይ እርምጃ ያለመውሰድ፣ የሳይት ተቆጣጣሪዎችን በበቂ ሁኔታ ያለመመደብ፣ አዳዲስ ሀሳቦችን በማፍለቅ አማካሪው ግንባታ እንዲፋጠን ጥረት ያለማድረግ ከሚታዩ ችግሮች ጥቂቶቹ እንዲሆኑ ጠቅሰዋል፡፡ አቶ ሙሉጌታ ፀሀይ ወርቄ በቤቶች ልማት ፕ/ጽ/ቤት የግንባታ ክትትልና ድጋፍ ም/ስራ አስኪያጅ በሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ባሉ አማካሪ ድርጅቶችና በነሱ ስር ባሉ ባለሞያዎች ዙሪያ እየታዩ ያሉ ችግሮችን በዝርዝር ካስቀመጡ በኋላ የአሁኑ ውይይትም ችግሮቹን ደረጃ በደረጃ በመፍታት ግንባታውን በማፋጠን በጉጉት የሚጠበቀውን ቤት ፈላጊ ችግር መፍታት አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ አማካሪዎቹ በበኩላቸው የተነሱት ችግሮች መኖራቸውን ተቀብለው ይሁን እንጂ በነሱም በኩል ያሉ ችግሮችን ተቋሙ ፈትሾ ሊፈታላቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል ከዚህም አንፃር በተለይም ከክፍያ መዘግየት ጋር በተያያዙ ባለሞያዎች እየለቀቁባቸው ስለመሆኑና የማቴሪያል አቅርቦቶች መጓተት፣ የኤሌክትሪክና የውሀ ችግሮች ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡና በነዚህ ችግሮች ሳቢያም ለግንባታ መጓተት ምክንያት እየሆነን ነው ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ችግሮችን እየፈቱ በመሄድ ቀጣይ ግንባታው በዘገየው ልክ ፈጥኖ መፍትሄ በማስቀመጥ ግንባታን ለማፋጠንና አጠናቆ ለመውጣት የጋራ መግባባት ላይ መድረሱን የፕ/ጽ/ቤቱ ኮሙኒኬሽን ስራ ሂደቱ ዘግቧል፡፡ Image may contain: sky, cloud and outdoor

Thursday, April 4, 2019

በሙስና ምንነትና መከላከያ ስልቶች ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ መጋቢት 2011 ዓ.ም ዜና የፀረ-ሙስና ትግሉን ለማጠናከር የህብረተሰቡን ግንዛቤ ይበልጥ ማዳበር እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽ/ቤት ሠራተኞች በሙስና ምንነትና መከላከያ ስልቶች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂደዋል፡፡

Tuesday, February 5, 2019

በየደረጃው የሚገኙ ባለሙያዎችና የአመራር አካላት መብትና ግዴታቸውን አውቀው የየተቋማቱን ዕቅድ ለማሳካት እንዲችሉ በሰራተኞች የመተዳደርያ ደንብ ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ ተጠቆመ ፡፡ ለአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ፅ/ቤት እና በስሩ ለሚገኙ 18 ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች የሰው ሃብት ሰራተኞች እና አመራሮች ስልጠና ተሰጥቷል ፡፡ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት የሰው ሃብት አስተዳደር ደጋፊ የስራ ሂደት መሪ አቶ ጃምቦ ብርሃኑ ለሁለት ቀናት በተሰጠው ስልጠና ላይ ባደረጉት ንግግር በየወቅቱ የሚዘጋጁ ዕቅዶችን በአግባቡ በመተግበር ተቋማቱ የቆመለትን ግብ ለማሳካት ሰራተኞች መብትና ግዴታቸውን አስመልክቶ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመዋል ፡፡ አንዳንድ ሰራተኞች በሰራተኞች መተዳደርያ ደንብ ዙርያ በቂ ግንዛቤ የሌላቸው በመሆኑ በዚህ ሳቢያ የተፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት ታስቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡ አቶ ጃምቦ ብርሃኑ ህጉን አስመልክቶ የግንዛቤ ማነስ ናቸው ያሏቸውን በአግባቡ አለመተርጎም ቅሬታ አቀራረብ እንዲሁም አዲስ ተቀጣሪ ሰራተኞች ክሊራንስ እንዲያቀርቡ ሳይደረግ መቅጠር፤ ከሰው ሃብት የስራ ሂደት ዕውቅና ውጪ የስራ ሃላፊዎች ዝም ብሎ ደረጃ ዕድገት መስጠት ዋና ዋና ችግሮች መሆናቸውን ገልፀው ከሰራተኛው የሚጠበቁ ተግባራትንም አብራርተዋል፡፡ ሰልጣኞችም በበኩላቸው በሰው ሃብት አስተዳደር መሰራት ያለባቸውና ሰራተኛው ማወቅ አለበት ያሉትን ተግባራት በስልጠናም ሆነ በተለያየ መንገድ ግንዛቤያቸውን ማሳደግ ይገባል ማለታቸውን የዘገበው የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት የኮሙኒኬሽን ደጋፊ የስራ ሂደት ነው ፡፡

Thursday, January 31, 2019

ዜና በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ፅ/ቤት በመገንባት ላይ ያሉ ቤቶችን አጠናቆ ለተጠቃሚዉ ለማስተላለፍ የክትትልና ድጋፍ ስራዉ ሊጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ፡፡ የ2011 የመጀመሪያ 6ወር ቢኤስ ሲ እቅድ አፈፃፀም ምዝና ለማካሄድ በተዘጋጀ ቲኦር ላይ ከየስራ ሂደቱ እና ከቅ/ፕ/ፅ/ቤቱ ለተወጣጡ መዛኝ ባለሙያዎች ኦረንቴሽን ተሰጥቷል፡፡ የክትትል ድጋፍና ምዘና ደጋፊ የስራ ሂደት መሪ አቶ ሰለሞን ንዳ በኦረንቴሽኑ ላይ ባቀረቡት ሰነድ እንደገለፁት ምዘናዉ የሚደረገዉ የማዕከል የስራ ሂደቶች፣ 17 ቅርንጫፍ ፕሮጀክት ፅ/ቤቶችና የአግሮስቶን ፋብሪካ የስራ ክፈሎቹ ከዋና ስራ አስኪያጅ ጋር የተፈራረሙት የ2011 ቢኤስሲ እቅድ መሠረት አድርጎ ነው፡፡ የምዘና ሂደቱ ከጽ/ቤቱ ሠራተኞች በተጨማሪ የአማካሪ ድርጅቶች፣ የሥራ ተቋራጮችና የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማትን እንደሚያካትት ገልፀው 121 ዋና፣ንዑስ እና ደጋፊ ያሥራ ሂደቶች እናዲሁም በማዕከል እና በቅርነጫፍ የሚገኙ 236 ኬዝ ቲሞች በምዘናዉ ዉስጥ እንዲያልፉ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ከ2400 በላይ ፈፃሚዎች ተሳታፊ እንደሚሆኑም አክለው ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ ሰለሞን ገለፃ በዋና ስራ አስኪያጅ የሚመራ አብይ ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን 6 ቡድኖች እንዲቋቋም ተደርጓል፡፡ የምዘና ቡድኖቹም በየሁለት ቀኑ የግንኙነት ጊዜ ተቀምጦላቸው ሥራዎች የሚገመግሙ ይሆናል፡፡ ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ በ2011 የቢኤስሲ ዕቅድ መሠረት ታህሳስ ለማጠናቀቅ በእቅድ የተያዙ ቤቶች አፈፃፀም በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ከመገምገም በተጨማሪ ሁሉም ፈፃሚዎች በከተማ ደረጃ የተያዘውን አቅጣጫ በመከተል እንደሚመዝኑ ታውቋል፡፡ ይህም ሥራን ቆጥሮ የመስጠትና የመቀበል ባህልን እንደሚያዳብር መሆኑን በውይይቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ጽ/ቤቱ ከ94 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲሁም 1717 የኪራይ ቤቶች ግንባታ እያከናወነ እንደሚገኝ ከአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ፅ/ቤት የኮሙኒኬሽን ጉ/ደ/የስ/ሂደት የደረሰን ዘገባ ያመለክታል፡፡

Monday, January 21, 2019

የተከበሩ ባለጉዳያችን ትክክለኛዉን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ፅ/ቤት መረጃ በሚከተሉት አድራሻዎቻችን ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እየገለፅን፡፡  የፌስቡክ ገፅ፡- Housing Development Project Office 20/80  የፌስቡክ አካዉንት፡- ቤቶች ኮሙኒኬሽን (የአዲስ አበባ ቤቶች ፕሮጀክት)  ብሎገር፡- ADDIS ABABA HOUSING PROJECT OFFICE  ዩ ቲዩብ፡- Addis Ababa housing Development project office  ቲዉተር፡- Addis Ababa Housing Development Project Office  ወርድ ፕረስ፡- Hdpo communication  የኢ-ሜይል አድራሻ፡- hdpocommunication@gmail.com  ዌብ ሳይት፡- www.http://www.aahdpo.gov.et/  ስልክ ቁጥር የኮሙኒኬሽን፡- 0118787940 በተጨማሪም ከላይ የተገለፀዉን የፈስ ቡክ ገጽ እና አካዉንት በማድረግ ሀሳብ አስተያየቶን ማንሸራሸር ይችላሉ እናመሰግናለን፡፡

Sunday, January 13, 2019

የመጀመሪያዉ መንፈቀ አመት ግምገማ

በመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ላይ ውይይት ጥር ቀን 2011 ዜና በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽ/ቤት ለ2011 በጀት ዓመት በዕቅድ የተያዙ የግንባታ ተግባራትን ለማሳካት የሚያስችል የተከለሰ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገለፀ፡፡ የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ባለሙያዎችና አመራሮች በመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ የፕሮጀክ ጽ/ቤቱ ሠራተኞች ባካሄዱት ውይይት ላይ እንደተገለፀው በ2011 በጀት ዓመት የመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት የሥራ ክንውን ላይ የተገኙ መልካም ውጤቶችና ያጋጠሙ ችግሮችን ታሳቢ ያደረገ የተከለሰ ዕቅድ በማዘጋጀት ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን ዕቅዱ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ያስችላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ኪሮስ መሰለ እንዳመለከቱት በተለያዩ ሳይቶች ግንባታቸው እየተፋጠነ ያሉት የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ተመዝግበው በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ለማድረስ እየተደረገ ያለው ርብርብ የሚበረታታና ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው ነው፡፡ የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የጥናት፣ ዕቅድና በጀት የሥራ ሂደት መሪ አቶ ተዘከር ፀጋዬ በውይይቱ ላይ ባቀረቡት የስድስት ወራት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት በተለይ ግንባታቸው ባለፈው የ2010 በጀት ዓመት የተጀመሩት ከአንድ ሺህ ሰባት መቶ በላይ ለኪራይ የሚቀርቡ ቤቶች በአሁኑ ወቅት ከ91 በመቶ በላይ መድረሳቸው መልካም ተሞክሮ በመሆኑ ወደ ሌሎች ግንባታዎችም ሊስፋፋ እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡ ሪፖርቱን ተከትሎ የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰነዘሯቸው አስተያየቶችና ጥያቄዎች መንገድ፣ መብራትና ውሃን የመሰሉ የመሠረተ ልማት አቅርቦቶች አለመሟላት እንዲሁም የግንባታ ግብዓት አቅርቦት እጥረትና ሌሎችም ተያያዥ ችግሮች ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ የጠቆሙ ሲሆን ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቿል፡፡ በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ያለው መልካም አስተዳደር በሚፈለገው ደረጃ እንዲሆን የህብረተሰቡን እርካታ መሠረት ያደረገ ፈጣን ምላሽ በመስጠት የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ ይበልጥ ጠንክሮ መሥራት እንደሚያስፈልግና በየደረጃው የሚገኙ ባለሙያዎችና ኃላፊዎችም ሥራቸውን በባለቤትነት ስሜት ማከናወን እንደሚጠበቅባቸው ተጠቁሟል፡፡ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽ/ቤት በተለያዩ ሳይቶች ከ94 ሺህ በላይ ቤቶች በመገንባት ላይ እንደሚገኝ የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ደጋፊ የሥራ ሂደት ዘግቧል፡፡